የፓርቲው አባል ግዴታዎች

ማንኛውም የፓርቲ አባል የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩበታል፡-

  1. በማንኛውም ጊዜና በየትኛውም ቦታ በፓርቲ ሕግ መሠረት የጸደቁትን የፓርቲውን ፕሮግራም፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ መመሪያዎች፣ ውሳኔዎችና ዕቅዶችን የማወቅ፣
  2. የመቀበል፣ የማክበር፣ የመገዛት እና ለተግባራዊነታቸው በግንባር ቀደምትነት የመታገል፣
  3. በሚገኝበት የሥራ መስክ እና ኃላፊነት ደረጃ የፓርቲውን አንድነት፣ ጥራትና ጥንካሬ፣ የፓርቲውን የፖለቲካ ዕሳቤዎች ለመጠበቅ ሙሉ ተሳትፎ የማድረግ፣
  4. የፓርቲውን መርሆዎች፣ ዕሴቶችና የአባላትን የሥነ ምግባር ሕጎችን የማክበር እና የፓርቲውን የህዝብና የሀገርን ደኅንነትና ሉዓላዊነት የመጠበቅ፣
  5. የሀገሪቱን ሕጎች እና ልዩ ልዩ መንግሥታዊ ውሳኔዎችን ማክበር
  6. የፓርቲውን አንድነት፣ ጥራትና ጥንካሬ የሚጎዱ ማናቸውንም ዝንባሌዎችና ድርጊቶችን የማጋለጥና የመታገል፣
  7. በፓርቲው ውስጥ በግለሰቦች ወይም በቡድኖች የተያዙ ተናጠል ዐቋሞችን የፓርቲው በማስመሰል በማናቸውም መልኩ በሚዲያ ከማሠራጨት የመቆጠብ፣
  8. በአባላት መካከል የሚኖረውን መልካም ግንኙነት ከሚያጎድፍ ድርጊቶች የመታቀብ፣
  9. በዚህ ደንብ አንቀጽ 18 ንዑስ አንቀጽ 8/ተ/ እንደተገለጸው ማዕከላዊ ኮሚቴ በሚያወጣው የአባልነት መዋጮ ዓይነትና አከፋፈል መመሪያ መሠረት የአባልነት መዋጮ የመክፍል፣
  10. የፓርቲውን ንብረት በአግባቡ የመጠበቅ፣
  11. ከሙስና የጸዳ፣ ሙስናንና አድሎአዊ አሠራርን የመታገልና የማጋለጥ ግዴታ እና
  12. ከአንድ አካባቢ ወይም የሥራ ቦታ ወደ ሌላ አካባቢ ወይም የሥራ ቦታ በቋሚነት ለቅቆ ሲሄድ የለቀቀበትን እና የደረሰበትን የፓርቲ መዋቅር ማሳወቅ፣ የፓርቲውን ንብረት እና ሰነዶችን ለለቀቀበት አካባቢ የፓርቲ መዋቅር ማስረከብ አለበት።